የማሕበረሰቡን ሰላም እና ደህንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የሕዝቡን ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለመጠበቅ ምህረት ለመስጠት የሚያስችል ሁኔታ መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በየወቅቱ ለሚከሰቱ ከፍተኛ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ሕግን ለተላለፉ አካላት ምህረት የሚሰጥበትን ሁኔታ ማመቻቸት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
ምህረትን በተመለከተ ከሀገሪቱ የወንጀል ሕግ የተደነገገውን ከሕገ-መንግሥቱ ጋር በማጣጣም ምህረት የሚሰጥበትን ሥነ-ሥርዓት በሕግ መደንገግ በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•