መንግሥት ለሕዝብ አገልግሎት ለሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች መሬትን መጠቀሙ አስፈላጊ ስለሆነ፣
የአገሪቱ ከተሞች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደጉና የነዋሪዎችም ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ በከተሞቹ ፕላን መሠረት ለመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ ለመሠረተ ልማት፣ ለኢንቨስትመንትና ለሌሎች አገለግሎቶች የሚውል የከተማ መሬትን መልሶ ማልማት አስፈላጊ በመሆኑ፣ እንዲሁም በገጠር ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች መሬት አዘጋጅቶ ማቅረብ በማስፈለጉ፣
የመሬት ይዞታ እንዲለቀቅ ሲደረግ ለባለይዞታው የሚከፈለውን ካሣ ለመተመን እንዲቻል ግምት ውስጥ መግባት የሚገባቸውን መሠረታዊ መርሆዎች ለይቶ መወሰን በማስፈለጉ፣
ካሣውን የመተመን ሥልጣንና የመክፈል ኃላፊነት ያለባቸውን አካላት በግልጽ ለይቶ መወሰን በማስፈለጉ፣ የፌዴራል መንግሥቱ የመሬት አጠቃቀም ሕግ የማውጣት ሥልጣን እንዳለው በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 51 (5) በመደንገጉና ለሕዝብ ጥቅም የሚለቀቅ ንብረትን በሚመለከት በቅድሚያ ተመጣጣኝ ካሣ እንዲከፈል በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40 (8) የተቀመጠውን መሠረተ ሃሳብ በመመርኮዝ በዝርዝር መደንገግ በማስፈለጉ፣
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት ታውጇል፡፡
•
•