ለስኳር ኢንዱስትሪ ልማት ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውል ተጨማሪ 47 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር (አርባ ሰባት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር) የሆነ ገንዘብ የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በሕንድ የኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ መካከል እ.ኤ.አ ኤፕሪል 12 ቀን 2012 በኒውዴልሂ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 21 ቀን 2004 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•