መንግሥታዊ እና የግል የሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ በሥራ ስምሪት አገልግሎት አሰጣጥ የሚኖራቸውን ሚና በሕግ መወሰን በማስፈለጉ፤
በተለይ ወደ ውጭ አገር ለሥራ የሚሄዱ ኢትዮጵያዊያን መብታቸው፣ ደኅንነታቸውና ክብራቸው ተጠብቆ ባላቸው ችሎታና አቅም በይበልጥ የሚሠሩበትን ሁኔታ ማመቻቸት በማስፈለጉ፤
ሥራና ሠራተኛ በማገናኘት ሥራ በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር የሥራ ስምሪት ላይ የሚደረገውን የክትትልና ቁጥጥር አሠራር ሥርዓት ለማጠናከር በሥራ ላይ ያለውን የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ አዋጅ ቁጥር 104/1990 በተሻለ ሕግ መተካቱ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ- መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•