የፍትህ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የአንድ ጀምበር አርንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ- ግብር ተካሄደ

The Ministry of Justice and Affiliated Institutions Conduct One-Day Green Legacy Tree Planting Program

የፍትሕ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በአገር አቀፍ ደረጃ በዛሬው እለት የተካሄደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተከትሎ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ካራ መድሐኒያለም አቅራቢያ ተገኝተው 12 ሺህ ችግኞችን ተክለዋል።

ከዓመት ዓመት ባህል እየሆነ የመጣውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለትውልድ የሚጠቅም ስራ ለመሥራት ሁሉም የመርሀ ግብሩ ተሳታፊዎች ዘንድሮም በለሚኩራ ተገኝተው እያንዳንዳቸው የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ፍትሕ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የዘንድሮን የክረምት በጎ አድራጎትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ከዚህ ቀደም በጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በመገኘት የተለያዩ በጎ ተግባራትን ማከናወናቸውና 10 ሺህ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን ችግኞች መትከላቸው የሚታወስ ነው።

Tagged Under: Affiliated Institutions afforestation charity work Community Engagement environmental conservation Gambella Region gideon gideon timotheos green green legacy initiative initiative institutions kura legacy lemi lemi kura planting Public Service reforestation sustainable development timotheos tree Tree Planting
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

ተመሳሳይ ዜናዎች