በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ሕግ ሥነ- ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አወጣጥ ሒደት ዉስጥ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተጫወቱት ሚና ምስጋና ቀረበ

Members of the House of Peoples' Representatives Commended for Their Role in Drafting the FDRE Criminal Procedure and Evidence Law

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍትሕ ዘርፉን ከመደገፍ አንፃር በተከናወኑ ተግባራት እና በቀጣይ ትኩረት ሊደረግባቸው በሚገቡ ጉዳዮች ዙሪያ የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሜ በደዎን ጨምሮ የመንግስት ረዳት ተጠሪ፣ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ አባላትና ሌሎች የምክር ቤቱ አባላት፣ የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሐና አርአያስላሴ፣ ሚኒስትር ዲኤታዎች ፤የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች የተቋሙ አመራሮች በተገኙበት ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት ተካሂዷል።

በዚህ ወቅት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሜ በደዎ እንደገለፁት የፍትሕ ስርዓቱን ለማዘመንና ተደራሽ ለማድረግ ብሎም የጎደለውን ለመሙላት በምክር ቤቱ የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየቱን ገልፀው የተሰሩ ስራዎችን በዚህ ልክ በየምዕራፉ በመፈተሽ የተገኙ ውጤቶችን እያላቁ መሄድ የሚኖረው ትርጉም የጎላ እንደሆነ አንስተዋል፡፡

አያይዘዉም በምክር ቤቱ ከፀደቁ 1400 በላይ ሕጎች ዉስጥ 200 ያህሉ ከለዉጡ ወዲህ የወጡ መሆናቸዉን ጠቁመዉ ከእነዚህ ሕጎች ዉስጥ የወንጀል ስነ-ሥርዓትና የማስረጃ አዋጅ 1410/2018 ዋነኛዉ መሆኑን ያነሱት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ ህጉ ከመፅደቁ በፊት የወሰደዉ ጊዜ ቀላል የማይባልና የምክር ቤት አባላቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሰፊ ጊዜያቸዉን ሰጥተዉና ሰፊ ዉይይት በማድረግ የሕዝብን የፍትሕ ጥያቄ ለመመለስ በሚያስችል መልኩ ሊወጣ መቻሉን አንስተዉ ለዚህ አዋጅ መሳካት አስተዋፅኦ ያደረጉ የሕግና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴ፣ ለፍትሕ ሚኒስቴርና ለሌሎች የምክር ቤቱ አባላት ብሎም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና በማቅረብ በቀጣይም የበቁና ወቅቱን የዋጁ ሕጎች ለማዉጣት ሰፋፊ ጥረት የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሐና አርአያስላሴ በበኩላቸዉ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተደረጉ የፍትሕ ማሻሻያ ስራዎች በተለይም የሕዝቡን ውክልና ያረጋገጠና የአስፈፃሚ አካላት ሚና በሕግ የተገደበ መሆኑንና የሕዝቡን ውክልና ያረጋገጠ በማድረግ ረገድ ምክር ቤቱ የነበረው ሚናና ያበረከተው አስተዋፅኦ እጅጉን የጎላ እንደነበር ገልፀዋል ።

አክለውም ምክር ቤቱ በፍትሕ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ትግበራ በተለይም የባሕላዊ የፍትሕ ስርአት እውቅና እንዲያገኙና እንዲተገበሩ በማድረግ የነበረው ክትትል፣ የአስተዳደር ስነ-ስርዓት ሕጉ በፌደራልና በክልሎች እንዲተገበሩ በማድረግ ሂደት የነበረው ሚና ፣ መሠረታዊ የሕግ ማሻሻያዎች የተደረጉበት እና በተለይም በቅርቡ የፀደቀውን የወንጀል ስነ-ስርዓትና የማስረጃ ሕግ እንዲወጣ ምክር ቤቱ ያደረገው አስተዋፅኦ እጅጉን የሚያኮራ እንደነበር በመግለፅ ለዚህም ከፍተኛ አክብሮትና ምስጋና አቅርበዋል።

በተጨማሪም የወንጀል ስነ-ስርዓትና የማስረጃ ሕግ ይዞት የመጣውን የወንጀል ፍትሕ ፓሊሲ በተሟላ መልኩ ለመተግበር የሚያስችል ዝርዝር የአፈፃፀም ዕቅድ ወጥቶ ወደስራ መግባቱ ተገልፆል።

በዉይይቱ ላይ የህሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍትሕ ዘርፉን ከመደገፍ አንፃር የነበረዉ ሚና፣የተገኙ ዉጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎችን በሚመለከት በፍትሕ ሚኒስቴር የመንግስት ሕግና ፍትሕ አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አቶ በላይሁን ይርጋ አማካኝነት ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን፤ የምክር ቤቱ ሚና በሆኑት የህግ ማውጣ፣ ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም በዉክልና ዙሪያ ያከናወኗቸዉን ተግባራት በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በነዚህ ተግባራት ዙሪያ ምክር ቤቱ የነበረዉ ሚና እጅጉን የሚበረታታና መሬት የረገጠ እንደነበር አንስተዋል፡፡

በጥቅሉ በቀጣይ የተሻለ የሕግ አወጣጥ ሂደትን በመከተልና አሰራሩን ዲጂታላይዝ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ተዓማኒነት ያለው የፍትሕ ስርዓት ለመገንባት የሕዝቡን የሕግ ግንዛቤ ለማሳደግ የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የተገለፀ ሲሆን፤ የሚወጡ ሕጎች ጥራታቸዉን የጠበቁና አሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ ሒደት ዉስጥ የምክር ቤት ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመላክቷል፡፡

Tagged Under: act african charter on the rights and welfare of the child criminal Criminal Procedure decree draft drafting Evidence Evidence Law fundamental law house law legislation member members peoples' Policy pro procedure proclamation Regulation representative Representatives res statute Use
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች