በኢ.ፌ.ዲ.ሪ.ፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ተስፋዬ ዳባ በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በመገኘት የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና በ2018 ዕቅድ ላይ ተወያዩ

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ.ፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ተስፋዬ ዳባ በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በመገኘት የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና በ2018 ዕቅድ ላይ ተወያዩ ● FDRE Ministry of Justice State Minister for Attorney General Affairs, H.E Ato Tesfaye Daba, Visits Dire Dawa Branch Office to Review 2024/25 Budget Year Performance and Discuss 2025/26 Plans

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ተስፋዬ ዳባ በድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት በመገኘት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የተገኙ ውጤቶች እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ለማሳካት የታቀዱ ግቦች ላይ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

በመድረኩ በ2017 በጀት ዓመት በታቀዱ ስራዎች የተገኙ ውጤቶች እንዲሁም በ2018 ለማሳካት የታቀዱ ስራዎች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን የተያዙ ግቦችን ከማሳካት ረገድ አመርቂ ውጤት የተመዘገበ መሆኑን ይህም የሚያበረታታ እና በ2018 በጀት ዓመት ለታቀዱ ተግባራት እንደ ጥሩ መነሻ የሚወሰድ መሆኑን በተሳታፊዎች ተነስቷል፡፡

በውይይት መድረኩ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው እንደገለጹት ባለፈው 2017 በጀት ዓመት በፍትሕ ዘርፍና በተቋም ደረጃ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት መመዝገቡን በማንሳት በ2018 በጀት ዓመት የተያዙ ግቦችን ለማሳካት እና በተሻለ ሁኔታ ለመፈፀም ሁሉም የጽ/ቤቱ አመራሮች እና ሠራተኞች በዕቅድ የተያዘውን ተልዕኮ ለማሳካት መትጋት እንዳለባቸው እና ባለፈው በጀት ዓመት ያልተሳኩ ጉዳዮች ለማሳካት ትኩረት በመስጠት መሥራት እንደሚገባቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

በቀጣይ ቀናት ከድሬዳዋ ፖሊስ ጋር በጋራ የሚሰሩ የምርመራ፣ የክስና ክርክር ተግባራትን በሚመለከት የአፈፃፀም ግምገማ የሚደረግ ይሆናል፡፡

የቅርብ ጊዜ ዜናዎች