በተሻሻለው የፀረ-ሙስና ልዩ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 434/1997 ውስጥ ግልፅነት የጎደላቸውን ድንጋጌዎች ግልፅ በማድረግ ማሻሻል እና አዳዲስ ድንጋጌዎችን ማካተት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
የሙስና ወንጀልን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ውስጥ በሙስና ወንጀልነት እንዲካተቱ የተደረጉ የተወሰኑ የህዝባዊ ድርጅት አካላትን በሥነ-ሥርዓትና በማስረጃ ሕጉም ማካተት አስፈላጊ በመሆኑ፤
ሙስና ወንጀልን በሚመለከት መረጃ የመሰብሰብ፣ የምርመራ፣ የክስ፣ የክርክር፣ በሙስና የተገኘ ሀብት ወይም ተመጣጣኙን የማገድና የማስመለስ ወለስ ሥራ ቀልጣፋና ውጤታማ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ገ-መንግስት አንቀፅ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•