የተጎሳቆለ መሬት መልሶ እንዲያገግም በማድረግ፣ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ደኖችን በመጠበቅና በመንከባከብ ለሀገራችን ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚያዊ፤ ማህበራዊና የሥነ-ምህዳር ጥቅም እንዲሰጥ ማድረግ በማስፈለጉ፤
ለአረንጓዴ አሻራ ሥራዎች ቋሚና ተቋማዊ ሥርዓት ያለው የፋይናንስ አቅም እንዲኖር ማስቻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ በዘላቂነት የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም እና ከአየር ንብረት ብክለት የፀዳ ኢኮኖሚ ለመገንባት የተያዘውን ሀገራዊ ራዕይ እንዲሳካ አስተዋፅኦ ማድረግ በማስፈለጉ፤
እነዚህን ዓላማዎች ተግባራዊ ለማድረግ የተቀናጀ ቋሚና ዘላቂነት ያለው የሀገር ውስጥ የፋይናንስ ምንጭ በመመደብና በማሰባሰብ ሁሉም ክልሎች ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አሰራር መቀየስ ተገቢና ለዚህም የአረንጓዴ አሻራ እና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•