ፀረ-ተባይ ለተለያዩ አገልግሎቶች ማለትም ለሰብል ምርት፣ ለእንስሳት ልማት፣ ለሕዝብ ጤና ጥበቃ አገልግሎት መጠቀም በቀጣይነት እያደገ በመምጣቱ፤
ፀረ-ተባይ በሰው ልጆች፣ በእንስሳት፣ በዕፅዋትና በአካባቢ ላይ የሚያሳድሩትን ጎጂ ተፅዕኖ መቀነስ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤
ፀረ-ተባይን የማምረት፣ የማዘጋጀት፣ ወደአገር ውስጥ የማስገባት፣ ወደ ውጭ አገር የመላክ፣ የማጓጓዝ፣ የማከማቸት፣ የማከፋፈል፣ የመሸጥ፣ የመጠቀም፣ የማስወገድና ከነዚሁ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሌሎች ተግባራት ለመቆጣጠር የሚያስችል የተሟላ ሕግ ማውጣት በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•