ለሀሙሲት-እስቴ የመንገድ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል መጠኑ 20 ሚሊዮን (ሃያ ሚሊዮን) የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በነዳጅ አምራችና ላኪ አገራት ፈንድ ለዓለም አቀፍ ልማት መካከል እ.አ.አ ኖቬምበር 9 ቀን 2016 በቪየና የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥር 30 ቀን 2009 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55(1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡