በፍትሕ ሚኒስቴር የንቃተ ሕግ ፣ትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የስታትስቲክስ እና ዳታ ኢንኮደር ባለሙያዎች ”Fundamental of Statics, Data Preparation, and Analysis Using Excel Spread Sheet” በሚል የሥልጠና ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 19- 21/2017 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጠው ሥልጠና ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል፡፡
የሥልጠና መድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የንቃተ ሕግ ፣ትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የምክትል ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ተክለ ልብሰወርቅ እንደተናገሩት ለተቋሙ የስታትስቲክስ እና ዳታ ኢንኮደር ባለሙያዎች ስለጠናውን መስጠት ያስፈለገው በስራ ላይ የሚስተዋሉ የክህሎት ክፍተቶችን ለመሙላት፣ በተቋሙ ውስጥ ወጥ የሆነ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት እንዲኖር ለማስቻል እንዲሁም ደንበኛ ተኮር የሆነ አገልግሎት ለመስጠት አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ነው ብለዋል፡፡ አክለውም ይህን መሰል ሥልጠና መስጠቱ የተደራጁ መረጃዎችን በአግባቡ ለመተንተንና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ለማስቻል ከዚያም ባለፈ የባለሙያዎች የስራ ላይ መነቃቃትን ለመፍጠርና የስራ ተነሳሽነታቸውን ለመጨመር የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡
በሥልጠና መድረኩ በገለጻ መልክ የቀረቡ ርዕሰ ጉዳዮችን መሠረት በማድረግ ሰልጣኞች የተግባር ልምምድ የሚያደርጉ በመሆኑ የተሻለ ግንዛቤን እንደሚፈጥር ተመላክቷል፡፡