በሴቶች እና ሕፃናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን መረጃ ለመመዝገብ ለሚያስችለዉ ሲስተም ተግባራዊነት አጋዥ የሚሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገ

Equipment Donated to Support System for Tracking Crimes Against Women and Children

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ተግባራዊ እያደረገ ያለዉን በአገር ዓቀፍ ደረጃ በሴቶች እና ሕፃናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን መረጃ ለመመዝገብ የሚያስችለዉን ሲስተም ተግባራዊነቱን ይበልጥ ለማጠናከር አጋዥ የሚሆኑ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ቁሳቁሶች ድጋፍ ከ.ዩ.ኤን.ውሜን(UN-WOMEN) በኩል ሚያዝያ 6/2028 ዓ.ም ተደርጎለታል፡፡

የተደረገዉ የቁሳቁስ ድጋፍ በተለይም ሲስተሙን ተግባራዊ ለማድረግ በሙከራነት በፌዴራልና በክልል ደረጃ እየተተገበረ ላለዉ ስራ የሚኖረዉ ሚና ከፍተኛ መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፣ ሲስተሙ በአገር አቀፍ ብሎም በክልል ደረጃ የሚያበረክተዉ አስተዋፅኦ የጎላ መሆኑ ተገልጿል።

በሴቶች እና ሕፃናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች መረጃ በተሟላ ሁኔታ መያዙ ቀጣይነት ላለዉ ዕቅድ፣ለበጀት እና ለፖሊሲ አዉጭዎች የሚኖረዉ ጠቀሜታ ትልቅ በመሆኑ፣ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ሲስተሙን ተግባራዊ ከማድረግ ጋር ተያይዞ የሚያስፈልገዉ ቁሳቁስም ሰፊ እንደሆነና ይህንኑ ለማሳካትም በቀጣይ ጉዳዩ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በተጠናከረና በተናበበ መልኩ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

በዛሬዉ ዕለት በዩ.ኤን.ውሜን በኩል ግምታቸው ስምንት ሚሊዮን ብር የሆነ ዴስክ ቶፖች፣ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ስካነር፣ የድምፅ ሪከርደር፣ የፎቶ ካሜራ እና ሲግኒችር ፓዶች ድጋፍ የተደረገ ሲሆን ትብብሩ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

ርክክቡ የፍትሕ ሚኒስቴር የተቋም ግንባታና ሪፎርም ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ኤርምያስ የማነብርሃን (ዶ/ር) እና የዩ.ኤን.ውሜን ኢትዮጵያ ተወካይ ሚስ ጃኔት ኪም በተገኙበት ተካሂዷል።

Tagged Under: african charter on the rights and welfare of the child against and healthcare administration and control authority arra (agency for refugees and returnees affairs) charge child child support children convention on the elimination of all forms of discrimination against women (cedaw) Crime Crimes Crimes Against Children crimes against humanity Crimes Against Women criminal equipment financial system safety and soundness gains harmonized commodity description and coding system medicine and healthcare administration and control authority offense port Prosecution support system tracking un women Women and Children
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

ተመሳሳይ ዜናዎች