አሁን በሥራ ላይ ያለው የሽያጭ ታክስ የሽያጭ እንቅስቃሴ በተከናወነ ቁጥር በሚፈጠረው ተጨማሪ እሴት ላይ ታክስ መሰብሰብ ስለማያስችል፣
የተጨማሪ እሴት ታክስ፡ ታክስን ላለመክፈል የሚደረገው ጥረት የሚያስከትለውን ጉዳት ለመከላከል እንዲሁም ግብር ከፋይ ያገኘውን ትርፍ ለማረጋገጥ ስለሚረዳ፣
በካፒታል ዕቃዎች ላይ የማይጣል የፍጆታ ታክስ በመሆኑ ቁጠባንና ኢንቬስትመንትን ስለሚያበረታታ፡
የሽያጭ ታክስ በተጨማሪ እሴት ታክስ መተካት ለኢኮኖሚው ዕድገት የሚያግዝና የመንግሥት ገቢ ከጠቅላላ ምርት ጋር ያለውን የመጠን ግንኙነት የሚያሳድግ ስለሆነ፣
በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 55(1)እና (11) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•
•
•
•