በአገልግሎት ላይ

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ

ቁጠባንና ኢንቨስትመንትን የማበረታታት ሚና ያለው፤ የካፒታል ዕቃዎችን ሳይጨምር በዕቃ እና አገልግሎት ፍጆታ ላይ የተጣለው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ከወጣ ወዲህ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ረገድ የተደረጉ ለውጦችን በተለይም የኤሌክትሮኒክ ግብይትን እና በዓለም አቀፍ ደረጃም ተቀባይነት ያገኙ አዳዲስ እሳቤዎችን በሀገራችን የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት ታክሱ ለኢኮኖሚው ዕድገት የሚፈለገውን እገዛ እንዲያደርግ ማስቻል ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ፤

መሰረታዊ የሆኑ የተጨማሪ እሴት ታክስ ድንጋጌዎችን በአዋጁ ውስጥ በማካተት እና ዝርዝር ድንጋጌዎችን ለደንብና መመሪያ በመተው አዋጁ በቀላሉ ለመረዳት የሚያስችል አወቃቀር እንዲኖረው እንዲሁም ለአፈጻጸም ግልጽ እና ምቹ እንዲሆን ማድረግ በሚያስችል አኳኋን መቅረጽ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤

ከታክሱ ነጻ የመሆን መብት አተገባበር የመብቱ ተጠቃሚ እንዲሆን የታሰበውን የህብረተሰብ ክፍል ማእከል ያደረገ እና በግብአት ታክስና በውጤት ታክስ መካከል ያለውን ሰንሰለት የጠበቀ እንዲሆን በማድረግ ፍትሐዊነትንና የዜጎችንም ሆነ የንግድ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በማስፈለጉ፤

በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 99 መሠረት ሚያዝያ 3 ቀን 1994 ዓ.ም በተካሄደው የፌደሬሽን እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቶች 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ የጋራ ስብሰባ እና በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት በተሰጠ ሥልጣን የሚከተለው ታውጇል።

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 1341/2016
ቀን: ነሐሴ 25፥ 2016 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች

570/2017

መጋቢት 08÷ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1157/2011

ነሐሴ 7፥ 2011 ዓ.ም.
የተሻረ
አዋጅ ቁጥር 609/2001

ታኅሣሥ 16፥ 2001 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 79/1995

ታህሳስ 22፥ 1995 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 285/1994

ሰኔ 27፥1994 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 285/1994

ሰኔ 27፥ 1994 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ