የአገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከፍ ለማድረግ የሚያስችል የወጪ ንግድ የቀረጥ ማበረታቻ ሥርዓት ለመዘርጋት የወጣው አዋጅ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ በወጪ ንግድ ሥራ ላይ የተሠማሩ ባለሀብቶችን የሥርዓቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያላደረገ ስለሆነ፣ በዚህ አዋጅ አፈጻጸም ሂደትም አንዳንድ ክፍተቶች የታዩበት በመሆኑ፤
ቀጥተኛ ያልሆኑ ላኪዎች የሥርዓቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ እና በአዋጁ አፈፃፀም የታዩ ችግሮችን ማስወገድ የወጪ ንግድ እንቅስቃሴን ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑ ስለታመነበት፤
በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 55(1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•
•
•