በአገልግሎት ላይ

በባንክ በመያዣ ስለተያዘ ንብረት የወጣ አዋጅ

በባንኮች በዋስትና የተያዙ የማይንቀሳቀሱና የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች እንዲሸጡ ለፍርድ ቤት ክስ አቅርቦ ለማስወሰንና ውሳኔውንም ለማስፈጸም የሚወስደው ጊዜ በጣም ረጅም በመሆኑ፤ 

በቁጠባ ሂሣብ መልክ ከሕዝብ የሰበሰቡትንና ከተለያዩ ምንጮች ያገኙትን ገንዘብ በማበደር በሚገኘው የወለድ ገቢ የሚተዳደሩ ባንኮች ሥራ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ በማሳደሩ፤

ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴው አመቺ ሁኔታ ለመፍጠር ባንኮች ለተለያዩ የንግድና የልማት እንቅስቃሴ የሚሰጧቸው ብድሮችን በተቀላጠፈ መንገድ ለመሰብሰብ እንዲችሉና ለወደፊቱ ጥሩ የንግድ አሰራር ባህል እንዲዳብር ለማድረግ ለባንክ ብድር በመያዣ የተሰጡ የማይንቀሳቀሱና የሚንቀሳቀሱ ንብረቶችን ሽያጭ በሚመለከት በሥራ ላይ ያሉትን ሕጎች ማሻሻልና አዲስ ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 97/1990
ቀን: የካቲት 12፥ 1990 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች

አዋጅ ቁጥር 1374/2017

ሰኔ 11፥ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 566/2016

ጥር 30፥ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1358/2017

ጥር 29፥ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 559/2017

ጥቅምት 18፥ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ