የሕዝብ በዓላት ለዜጎች ሥነ-ምግባርና ስነ-ልቦና ግንባታ እንዲሁም ለሀገርና ለህዝብ ያላቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ ለህዝባዊ በዓላት ሕጋዊ እውቅና መስጠት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
የሕዝብ በዓላት ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ታሪካዊ እሴታቸውን ጠብቀው በሰላም፣ በድምቀት እና የዜጎችን የእርስ በእርስ መልካም ግንኙነትና መተሳሰብ በሚያጎለብት ሁኔታ እንዲከበሩ ለማድረግ የህዝብ በዓላትን አከባበር በሕግ መደንገግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) እና 55 ንዑስ አንቀጽ (2) ፊደል ተራ (ረ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•