ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መጠናከር የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሉዓላዊነት፣ ሕገ- መንግሥትና የሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓትን ለመጠበቅና ለመከላከል አስፈላጊ በመሆኑ፤
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የአገሪቱን የሰላም፣ የልማት፣ የዲሞክራሲ እና የመልካም አስተዳደር ሥርዓት ግንባታ ለመደገፍ እንዲችል ሥልጣኑን፣ ተግባሩን እና ተጠያቂነቱን መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ፤
ለኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ- መንግሥትና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በታማኝነትና በጽናት የቆመ፣ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን ያገናዘበ፣ ዘመናዊና ጠንካራ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት መገንባት በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55(1) እና (7) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•