አንዳንድ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ጥረቶች ልማቱን የሚቀለብስ ጎጂ አካባቢያዊ ተፅዕኖ ሊያስከትሉ የሚችሉ በመሆናቸው፣
በአጠቃላዩ አካባቢን መጠበቅ በተለይም የሰውን ጤንነትና በጎ ሁኔታ እንደዚሁም የሕያዋንን ደሕንነትና የተፈጥሮን ሥነውበት ማቆየት የሁሉም ተግባርና ኃላፊነት በመሆኑ፣
የመከላከያ ወይም የማስወገጃ እርምጃዎችን በመውሰድ በማሕበራዊና በኢኮኖሚያዊ ልማት ጥረቶች ሂደት የሚከሰተውንና የማይፈ ለገውን ብክለት ማስወገድ ሳይቻል መከላከል ተገቢ በመሆኑ፣
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•