የዱር እንስሳትና በመኖሪያ አካባቢያቸው ላይ የሚደረግ የፊልም ቀረፃ የዱር እንስሳቱን አደጋ ላይ በማይጥልና ህጋዊ በሆነ መንገድ እነዲከናወን ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የዱር እንስሳት ኢ-ፍጆታዊ የአጠቃቀም ስልት አማካይነት ከዱር እንስሳት ሃብት የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በማጎልበት ለሀገሪቱ ልማት የሚያበረክተውን አስተዋጽዖ ማሳደግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
በዱር እንስሳት ፊልም ቀረፃ የሚስተዋሉ የአሠራር ክፍተቶችን በማስወገድ ወጥነት፣ ተጠያቂነት፣ ግልጽነትና ፍትሃዊነት የሰፈነበት የአሠራር ሥርዓት እንዲፈጠር ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
ቀደም ሲል የወጡትን የዱር እንስሳት፣ ጥበቃና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 541/1999 እና የዱር እንስሳት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 163/2001 ማስፈጸሚያ መመሪያ ማውጣት በማስፈለጉ፤
የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የዱር እንስሳት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 541/1999 አንቀጽ 17 (2) በተደነገገው መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡