በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሳተፉ የፌዴራል መንግስት ተቋማት ሠራተኞች ከመደበኛ የሥራ ሰዓት በኋላ እና በቅዳሜ ቀናት አገልግሎት በመስጠታቸው ምክንያት ተጨማሪ የመጓጓዣ ወጪ የሚገጥማቸው በመሆኑ፤ የአገልግሎት ቀጣይነትን፣ የሠራተኞችን ደህንነትና የሥራ ተነሳሽነት ለማጠናከር ፍትሃዊ፣ ግልጽ እና ተግባራዊ የሆነ የትራንስፖርት አበል አፈጻጸም ሥርዓት እንዲዘረጋ ማድረግን አስፈላጊ በመሆኑ፤ ኮሚሽኑ በመንግስት ሠራተኞች አዋጅ 1353/2017 አንቀጽ 156(2) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል።