የውሃ ልማት ፈንድ የብድር አሰጣጥና አወሳሰን መመዘኛዎችን በሕግ መምራት በማስፈለጉ፣ የፈንዱን የብድር አስተዳደር ሥርዓት ቀልጣፋና ለባለድርሻ አካላት ግልጽ ማድረግ በማስፈለጉ፣ የፈንዱን የብድር አሰጣጥ ሥርዓት ፍትሐዊ እና እኩል ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ መልኩ ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ በማስፈለጉ፣
የውሃ ልማት ፈንድን ለማቋቋምና አስተዳደሩን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 268/1994 (እንደተሻሻለ) አንቀጽ 7(2) እና 14(4) ለውሃ ልማት ፈንድ ቦርድ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህ መመሪያ ወጥቷል፡፡