የከተማ መሬት ይዞታ በአግባቡ መዝግቦ ለማወቅ የካዳስተር ቅየሳ መረጃ፣ አሠራር እና የቅየሳ መሣሪያዎችን አጠቃቀም በመወሰንና በሕግ በመደንገግ በአገር አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚነት ያለዉ ወጥ የሆነ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባን ለመደንገግ በወጣዉ አዋጅ ቁጥር 818/2006 አንቀጽ 54 ንዑስ አንቀጽ (2) መሠረት የከተማ ካዳስተር ቅየሳ ደንብ ቁጥር 323/2006ን ለማስፈጸም ይህን መመሪያ አውጥቷል።