ትምህርት የዕድገት ሁሉ ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ ለሁለንተናዊ ልማት መፋጠን ትልቁን ድርሻ ይይዛል፡፡ትምህርት ተመራማሪና ችግር ፈቺ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችልና የህብረተሰቡን አመለካከት ወደ እድገት አቅጣጫ የሚመራ ከአዳዲስ ቴክኖሎጂ ውጤቶች ሳይንሳዊ ግኝቶች ጋርበማስተዋወቅ ኢኮኖሚያዊ ማኅበራዊና ባህላዊ ዕድገቶችን የሚያፋጥን መሣሪያ ነው፡፡
ይህንን የትምህርት ሥራ ውጤታማ ለማድረግና የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማሳለጥ በየጊዜው አሰራሮችን ለማሻሻልና ለማዘመን በየትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ መምህራን ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮችን ሚና ከፍተኛ በመሆኑምመምሀራን እና የትምህርት አመራሮች ሙያዊ ሥነምግባርን በመላበስ ውጤታማ ሥራዎችን ማከናወን ይጠበቅባቸዋል፡፡በዚህ ረገድ አልፎ አልፎ በመምህራንና በትምርት ቤት አመራሮች የሚስተዋሉ የዲሲፕሊን ግድፈቶች ይታያሉ፡፡
ስለሆነምአሁን በስራ ላይ ያሉ መመሪያዎችን በመፈተሽ ወቅቱንየዋጀ ወጥነት ያለው መመሪያ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላትን እንደገና ለማቋቋም የወጣ አዋጅ ቁጥር፹፬/፪ሺ ፲፮ አንቀጽ ፲፮ ንዑስ አንቀጽ ፪(ሠ) እና አንቀጽ ፳፪ ሠሥልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡