የመመሪያ መለያ: 856/2014
ቀን: ታኅሣሥ 17፥ 2015 ዓ.ም.
Language: Amharic

የስፖርት ውርርድ ሎተሪ ፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 856/2014

የስፖርት ውርርድ ሎተሪን ጥብቅ በሆነ ሕግና ስርዓት እንዲመራ ማድረግና ቁጥጥሩን ማጠናከር በማስፈለጉ፣

ቀደም ሲል በነበረው መመሪያ ያልተካተቱ ተጨማሪ ክልከላዎች ማካተት በማስፈለጉ፣

የአዲስ ፈቃድ ማውጫ፣ የፈቃድ እድሳት ክፍያና የማኅበራዊ አገልግሎት ክፍያ ማሻሻል በማስፈለጉ፣

የአለም የስፖርት ውርርድ ሎተሪ ህጎች ከደረሰቡት የእድገት ደረጃ ጋር ተቀራራቢ ለማድረግና በአወራራጁና በተወራራጁ መካከል የሚነሱ አለመግባባቶችን ለመፍታት የሚያስችል መመሪያ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ የገቢዎች ሚኒስቴር የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደርን እንደገና ለማቋቋም በወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 160/2001 አንቀጽ 21 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የስፖርት ውርርድ ሎተሪ ፈቃድ መመሪያ ቁጥር 83/2005ን በዚህ መመሪያ አሻሽሏል፡፡

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF

ተጨማሪ መረጃዎች

መመሪያውን ያውርዱ

ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር

National Lottery Administration

Similar Directives

ሰኔ 18÷2018
ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር
Ministry of Trade and Regional Integration
ሰኔ 18÷2018
ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር
Ministry of Trade and Regional Integration