በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ስር የሚገኙ የመንግሥት ሆስፒታሎች ስተገልጋዩ ህብረተሰብ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት በማቅረብ ህብረተሰቡን ማርካት እንዲቻል የሥራ አመራር ተግባራት ብቃት ባለው አመራር እንዲመራ ማድረግ በማስፈስጉ፤
የሆስፒታሎችን የህከምና እና የበሽታ መከላከል ተግባራት በጥራትና ቅልጥፍና ስማከናወን በሙያቸው የሰለጠኑ ብቃትና ችሱታና ኖሯቸው ዕምነት የሚጣልባቸውን ግለሰቦች ወደ አመራርነት እና የአስተዳደርር ሥራ ኃሳፊነት በማምጣት በማስፈስጉ፤
የሆስፒታሎች ተቋማዊ ብቃትን በማሳደግ፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን የሚያስችል የአመራርና የአስተዳደር የሹመት ቦታዎች አቅምን ማዕከል ያደረገ አሳታፊ እና ግልፅ የሆነ ውድድር ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ማድረግ የሚገባ መሆኑ በመታመኑና የአሠራር ስርዓት መዘርጋት በማስፈስጉ፤
የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ በአዲስ አበባ አስተዲደር አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባራቸውን ስመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 74/2014 አንቀጽ 15 ንዑስ አንቀጽ (2) ተራ ፊደል (ሠ) መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡