ተቋሙ ከተቋቋመበት ዓላማ አንፃር ለከተማ ነዋሪዎች የላቀ የሚዲያ አገልግሎት ለመስጠት አድማጭን፣ ተመልካችንና አንባቢያንን ማዕከል ያደረጉ የሚዲያ ስራዎችን በማከናወን ተቋሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ በሰው ሐብት እየጎለበተ አደረጃጃቱና የሥርጭትም ሆነ የአገልግሎት ተደራሽነት አድማሱ እየሰፋ፤ከመዲናችን አዲስ አበባ በተጨማሪ ሌሎች የሀገሪቱ ክልሎች ተደራጅተዉ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ብቃት ላይ ለመድረስ የሚደረገውን ጥረት ተግባራዊ ለማድረግ የሰው ሃይል ልማትና የአፈጻጸም ብቃት ማዳበርበማስፈለጉ፤
የተቋሙን የሚዲያ የአገልግሎት ጥራት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርና የተወዳዳሪነት አቅሙን ለማሳደግ ብቃት ባለው የሰው ኃይል፣ አደረጃጀትና የአሠራር ሥርዓት መደገፍ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዲስ ሚዲያ ኔትወርክየሰራተኞች አስተዳደር ደንብ ቁጥር 5/2012 አንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ (1) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡