የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃን ገበያው የሚፈልገውን አቅምና ብቃት ያሟሉ መሆናቸውን ማረጋገጥ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በሀገራዊና ዓለማቀፋዊነት ገበያ ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉ ምሩቃንን በሁሉም የትምህርት መስኮች ለማፍራት እንዲቻል፤
ከአካባቢያዊ፤ ሀገራዊና ዓለማቀፋዊ ኢኮኖሚ፤ ቴክኖሎጂ ዕድገትና ከማኅበረሰቡ ፍላጎት ጋር እያደገ የሚሄድ ገበያ መር የትምህርት ስርዓተ በዘላቂነት ለመዘርጋት፤
የትምህርቱን ጥራት በማስጠበቅ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል ማፍራት በማስፈለጉ፤
ምሩቃን በእውቀት፤ ክህሎትና አመለካከት የበቁ መሆን አለመሆናቸውን ከተቀመጠው የምሩቃን ፕሮፋይል ጋር በመመዘን ማረጋገጥ ስለሚገባ፤
በፈተና አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ሌሎች የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላትን በአግባቡ ማሳተፍ አስፈላጊ በመሆኑ፤
በመሆኑም ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 1152/2011 አንቀጽ 95 ንዑስ አንቀጽ 2 እና አዋጅ ቁጥር 1263/2014 አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 2 መሠረት ይህንን የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና መመሪያ አውጥቷል፡፡