ከፍተኛ የሥራ ውጤት ያላቸውን ሠራተኞች ከፍ ወዳለ ኃላፊነት በማምጣት ሥራን የተሻለ አቅም ባላቸው ሠራተኞች ማሰራት አስፈላጊ በመሆኑ፤
የደረጃ እድገት የሥራን ውጤት ከማሻሻልም በላይ የሠራተኛውን የሥራ ፍላጎት የሚያነሳሳና ሠራተኛው በመ/ቤቱ ላይ ያለውን እምነት ከፍ የሚያደርግ በመሆኑ፤
በሥራ ውጤት ላይ የተመሰረተ የደረጃ እድገት ሥርዓት ሠራተኞች የሥራ ውጤታቸውን በየጊዜው ለማሻሻል ያልተቆጠበ ጥረት እንዲያደር የሚያበረታታ በመሆኑ፤
አስተዳደሩ የሚከተለውን የሠራተኞች የደረጃ እድገት አፈፃፀም መመሪያ አውጥቷል።