የመመሪያ መለያ: 140/2015
ቀን: ጥር 18፥ 2015 ዓ.ም.
Language: Amharic

የመንግስት ቤቶች አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 140/2015

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንብረት የሆኑትን የመንግሥት የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ትክክለኛ መረጃዎችን በማደራጀት፣ በተገቢዉ በማስተዳደር ዝቅተኛ ገቢ ያለዉ የህብረተሰብ ክፍል፣ወጣቶችን፣ሴቶችንና ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸዉን የአካል ጉዳተኞችን የቤት አስተዳደር ስርዓቱ ይበልጥ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ የአሠራርሥርዓት መፍጠር በማስፈለጉ፣

የከተማዉ አስተዳደር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህብረተሰቡን የመኖሪያ ቤት ችግርለማቃለል የመንግሥት ተቋማት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጀቶች፣ በባለሀብቶች፣ በህብረተሰቡ እና የበጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር የተገነቡ ለኪራይ የሚዉሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለማስተዳደር የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣

የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች በመልሶ ማልማት፣በተፈጥሮና ሰዉ ሰራሽ አደጋ ለሚነሱ ተነሺዎች ምትክ ስለሚሰጥበት ሁኔታ አሠራር መዘርጋት በማስፈለጉ፤

የአስተዳደሩ ቤቶች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አያያዝ እና አጠባበቅ ሁኔታ ለክትትልና ቁጥጥር አመቺ እንዲሆን በማድረግ በየጊዜዉ እየጨመረ የመጣዉን የመንግሥት ቤቶችን ያለአግባብ መጠቀምና ወደግል ይዞታ የማዞር ህገወጥ ተግባራትን በመግታት የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ በማስፈለጉ፣

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የከተማ አስተዳደሩን አስፈፃሚ አካላት ሥልጣንና ተግባራቸውን ለመወሰን ባወጣው አዋጅ ቁጥር 74/2014 አንቀጽ 19 ንዑስ አንቀጽ 3 እና በደንብ ቁጥር 11/1996 መሠረት ይህንን መመሪያ አዉጥቷል፡፡

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF

ተጨማሪ መረጃዎች

መመሪያውን ያውርዱ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

Addis Ababa City Administration Housing Development and Administration Bureau

Similar Directives

ሰኔ 18÷2018
ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር
Ministry of Trade and Regional Integration
ሰኔ 18÷2018
ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር
Ministry of Trade and Regional Integration