የመንግሥት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስና ለጡረታ ባለመብቶች ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የአሠራር ስልት መቀየስ አስፈላጊ በመሆኑ የመንግሥት መ/ቤቶችን እና ሠራተኞችን የምዝገባ ማስረጃ አደራጅቶ በመያዝ፣ ዘመናዊ የጡረታ መዋጮ አሰባሰብ ሥርዓት እንዲዘረጋ ፣ የጡረታ አበል ውሳኔ ሥራ በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲፈፀም ለማድረግ፣ እና የጡረታ አበል ለመወሰን የሚያስፈልጉ ዝርዝር ማስረጃዎችን ለፈጻሚው ግልፅ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ በተለያዩ ጊዜያት የወጡ መመሪያዎችን ማጠቃለል እና ከመንግሥት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 1267/2014 ጋር በማገናዘብ ማስተካከል ስለሚገባ በመንግሥት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 1267/2014 አንቀጽ 61/2/ ለአስተዳደሩ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የሚከተለው የመንግሥት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅ ማስፈፀሚያ መመሪያ ወጥቷል፡፡