የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማው ውስጥ የሚስተዋለውን የመኖሪያ ቤት ችግርለመቅረፍ የተለያዩ የቤት ልማት አማራጮችን በመንደፍ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይም የመንግሥት ሠራተኛውን ከተቀረጹት የቤት ልማት ፕሮግራሞች መካከል አንዱ በሆነው የመኖሪያ ቤት የኅብረት ሥራ ማኅበር በማደራጀት የመኖሪያ ቤት ችግራቸውን እንዲቀርፉ የሚያስችል ግልጽ የሆነ የማህበራት አደረጃጀት የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረት ሥራ ማኅበራት ኤጀንሲ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት እንደገና ለማደራጀት ሥልጣንና ተግባራቸውን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 74/2014 ዓ.ም አንቀጽ 15 ንዑስ አንቀጽ (2) ተራ ፊደል (ሠ) መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡