የጤና ሙያ ስነ-ምግባር ኮሚቴ ከጤና ባለሙያዎች የሙያ ብቃት ማነስ እና የስነ ምግባር ጉድለት እና ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚቀርቡ ቅሬታዎች ምርመራ እና የውሳኔ ሀሳብ አሰጣጥ ሂደትን በሕግ እና ሥርዓት መምራት በማስፈለጉ፤
የጤና ሙያ ሥነ ምግባር ኮሚቴውን ዝርዝር አሠራር፣ ተግባርና ኃላፊነት በሕግ በመወሰን የአሠራር ሂደቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን ማድረግ በማስፈለጉ፤
የጤና ሙያ ስነ ምግባር ኮሚቴን አሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የሕክምና ቅሬታ አቅራቢዎች ቀልጣፋ እና ፍትሃዊ ውሳኔ እንዲያገኙ እንዲሁም የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማረጋገጥ በማስፈለጉ፣
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጤና ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር 1112/2011 አንቀጽ 71 ንዑስ አንቀጽ 2 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል።