ማንኛውም ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ዛለቂ ልማትን ለማረጋገጥና የዜጎችን በንፁህና ጤናማ አካባቢ የመኖር መብትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ መከናወን ያለበት በመሆኑ፣
አካባቢያዊ እና ማኅበራዊ ተፅዕኖችን ለመተንበይ እና ለመለየት የሚከናወኑ ጥናቶች ጥራት ያላቸው እንዲሆኑ፤ ሙያዊ ብቃት እና የሙያ ስብጥር ባላቸው ባለሙያዎቸ እንዲጠኑ በማድረግ በልማት ውጥኖች እና ተግባራት ምክንያት ሊከሰቱ የሚችሉ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ለመከላከል ወይም ለመቀነስ ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑ፣
በአካባቢና ማኅበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ፣ በስልታዊ የአካባቢ ግምገማ እና በአካባቢ አዲት የማማከር አገልግሎት የሚሰማሩ ባለሙያዎችን እና ድርጅቶችን እውቅና ለመስጠት እና ለመቆጣጠር የሚያስችል መመዘኛ መስፈርት በማዘጋጀት ወጥነትና ተጠያቂነት ያለው የብቃት ማረጋገጫ አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፣
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር በአስፈፃሚ አካላት ሥልጣንና ተግባር መወሰኛ አዋጅ ቁጥር 1263/2014 አንቀጽ 19(4) እና በአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ አዋጅ ቁጥር 299/1995 አንቀጽ 7(2) እና አንቀጽ 20 መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡