ሠራተኛው ወደ ሥራ ቦታው የሚገባበትና ከሥራ የሚወጣበት የሥራ ቀናትና ሰዓት መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ፣ ለሠራተኛው በዕቅድ ላይ የተመሰረተ የዓመት እረፍት ፈቃድ በመስጠት ለተወሰነ ጊዜ በማረፍ አገልግሎቱን በታደሰ መንፈስ እንዲቀጥል ማስቻል አስፈላጊ በመሆኑ፤ ሠራተኛው በተለያዩ ምክንያቶች በፈቃድ ከመደበኛ ሥራ ስለሚቀር ወጥነትና ሥርዓትን የተከተለ የልዩ ልዩ ፈቃድ መመሪያ ማዘጋጀት በማስፈለጉ፤ አስተዳደሩ ይህንን የሥራ ሰዓትና ልዩ ልዩ ፈቃዶች መመሪያ አውጥቷል፡፡