በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ቁጥር 1113/2011 አንቀጽ 62 ንዑስ አንቀጽ (11) የማንኛውም ድርጅት አባል፣ አመራርና ሠራተኞች ሥራቸውን በሚያከናውኑበት ወቅት የድርጅቱን ጥቅም የማስቀደምና ከእነሱ ጥቅም ጋር እንዳይጋጭ ተገቢውን ጥንቃቄ የማድረግ ኃላፊነት እንዳለባቸው የተደነገገ በመሆኑ፤
በአዋጅ ቁጥር 1113/2011 አንቀጽ 20 (4) መሠረት ከድርጅቱ የስራ መሪዎች ጋር የስጋ እና የጋብቻ ዝምድና ያላቸው ሰዎች የቦርድ አባል ሆነው እንዳይሰሩ የተከለከለ በመሆኑ፤
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን በአዋጅ አንቀጽ 89 ንዑስአንቀጽ (2) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡
WHEREAS, Article 62, paragraph 11 of Civil Society Organizations Proclamation No. 1113/2019 provides that the members, management and employees of any organization have the responsibility of prioritizing the interests of the organization and taking due care not to conflict with their interests while performing their duties;
WHEREAS, according to Article 20 (4) of Proclamation No. 1113/2019, it is forbidden for people who are related by blood or marriage to the company’s officials to serve as board members;
NOW THEREFORE, the Civil Society Organizations Authority, as per the powers vested in it under Article 89(2) of the Proclamation, has issued this directive.