በሥራ ላይ ያለው የመንግሥት ሠራተኞች የቀን የውሎ አበል ተመን በሥራ ላይ ከዋለ ከአሥራ ሁለት ዓመታት በላይ ያስቆጠረ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት በክልሎች፣ በዞንና በወረዳ ከተሞች የሚገኙ ሆቴሎች ከሚያስከፍሉት የምግብና የመኝታ ዋጋ ጋር ሊመጣጠን ባለመቻሉ ለመስክ ሥራ በሚወጡ ሠራተኞች ላይ ከፍተኛ የወጪ ጫና በማሳደር በመስክ ሥራ ውጤታማነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ከማሳረፉም በላይ የሥራ ተነሳሽነትን በመቀነስ ለቅሬታና አቤቱታ ምክንያት በመሆኑ፣
በፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 አንቀጽ 12 ንዑስ አንቀጽ (4) የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን የአበል ዓይነቶችንና ክፍያዎችን እያጠና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ያቀርባል፣ ሲፈቀድም አፈፃፀማቸውን ይከታተላል በሚል በመደንገጉ፣
በሌላ በኩል የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው ደንብቁጥር 502/2014 አንቀፅ 4 ንዑስ አንቀፅ 14 ብቃት ያላቸውን የሥራ መሪዎችና ባለሞያዎችን ወደ መንግሥት መስሪያ ቤቶች ለመሳብና ለማቆየት የሚያስችል የክፍያ ሥርዓት እንዲኖር በየወቅቱ እያጠና ለመንግሥት ውሳኔ ያቀርባል፣ ሲፈቀዱም አፈፃፀሙን ይከታተላል፣ይቆጣጠራል በሚል በመደንገጉ፣
ኮሚሽኑ በፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 አንቀጽ 156 (2) መሠረት ለአፈጻጸም እንዲመች የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ይህን መመሪያ አውጥቷል።