በገበያ ዋጋ መርህ ባልተደረገ ግብይት ተሳታፊ በሆኑ ተዋዋዮች መካከል የተደረገው ማንኛውም ግብይት በትክክለኛ የገበያ ዋጋ የሚታየውን ገቢ፤ ጥቅም፤ ተቀናሽ፤ ኪሳራ ወይም ማካካሻ ተከትሎ እንዲወሰን ለማድረግ የሚደረገው ማንኛውም ክፍፍል ወይም ድልድል የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ መሠረት እንደሚከናወን በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ የተደነገገ በመሆኑ፤
ዓለም አቀፍ መልካም ተሞክሮዎችን በተለይም ደግሞ የዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ትብብር ድርጅት የማሸጋገሪያ ዋጋ መመሪያዎችን መሠረት ያደረገና የገበያ ዋጋ መርህን ሥራ ላይ ለማዋል የሚያስችል፣ ሁሉን አቀፍ የሆነ በማሸጋገሪያ ዋጋ የሚደረግ ግብይትን ለመቆጣጠር የሚያስችል አሠራር መዘርጋት በማስፈለጉ፣ በፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 79 (2) እና (4) ለገንዘብ ሚኒስትሩ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህ መመሪያ ወጥቷል፡፡