በሀገራችን የግንባታ ዘርፍ ማደግን ተከትሎ የሲሚንቶ ገበያ በተስያዩ ውጫዊና ውስጣዊ ምክንያቶች በአቅርቦትና ፍላጎት መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ በመምጣቱ ሥርጭቱ እየተስተጓጎለ እና የዋጋ ንረቱ እየተባባሰ በመምጣቱ የሲሚንቶ ገበያውን ስማረጋጋት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሲሚንቶ ግብይትና ስርጭትን አስመልክቶ ያወጣው የአሠራር መመሪያ ቁጥር 908/2014 በተግባር ሲፈተሽ ሲሚንቶን በቀጥታ ከፋብሪካው የመግዛት እድል ያገኙ አካላትና ተጠቃሚዎች በዋጋም ሆነ በአቅርቦት ተጠቃሚ መሆን የቻሱ ቢሆንም በተመረጡ አቅራቢዎች ለህብረተሰቡ እንዲደርስ የተደረገው የሲሚንቶ ሥርጭት የተጠቃሚውን ፍላጎት ያላሟላ ከመሆኑም በላይ ለተለያዩ ህገወጥ አሠራሮች የተጋለጠ መሆኑን በመገንዘብ፤
በአሁኑ ወቅት ሥራ ሳይ ያሰው የሲሚንቶ የሥርጭት ሥርዓት አፈፃፀሙ በርካታ ክፍተቶች ያሱበት በመሆኑ የተሻስ መፍትሄ እንዲበጅ ከህብረተሰቡና ከተሰያዩ አካላት የቀረቡ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን በግብዓትነት በመውሰድ፤
በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በኩል በተካሄደው የአፈፃፀም ፍተሻ ጥናት በተሰዩ ችግሮችና የመፍትሄ ሐሳቦች ላይ በሲሚንቶ ዘርፍ ከተሰማሩት ባስሀብቶችና ከሚመሰከታቸው የክልሎችና የከተማ አስተዳደር የሥራ ሃላፊዎች ጋር በተደረገው ውይይትም ሥራ ለይ ያስውን አሠራር ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን በመግባባት፤
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የአስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1263/2014 አንቀጽ 19 (4) መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡