በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ላይ በተገልጋዮች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች መፍትሄ በመስጠት የግልፀኝነት፣ የተጠያቂነት እና የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ አስፈላጊ በመሆኑ፤
በአገልግሎት አሰጣጥ ለቅሬታ መንስኤ የሚሆኑ ስህተቶችን ለማረምና አገልግሎት አሰጣጡን በተከታታይ ለማቀላጠፍና ውጤታማ ለማድረግ የሚረዳ የመረጃ ምንጭ ሆኖ የማገልገል እንዲሁም ለሌሎች ለሚመለከታቸው ህጋዊ አካላት አቤቱታ የማቅረብ ጫናን በመቀነስ እነዚህን ከላይ የተመለከቱትን ዓላማዎች በትክክል በተግባር ለማዋል እንዲቻል ይህንን መመሪያ ማውጣቱ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ እና ማዘጋጃ ቤት አገልግሎት አካላት እንደገና ማቋቋሚያ እዋጅ ቁጥር 35/2004 አንቀጽ 53 ንዑስ አንቀጽ 2 መ/ቤቱ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡