በእርቅ ማለቅ የሚችሉ ወንጀሎችን የወንጀል ምርመራ ከመጣራቱ በፊትም ሆነ ምርመራ ከተጣራ በኋላ ወይም ክስ ከተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን በእርቅ መጨረሱ ወጪ ቆጣቢ፣ አስተማሪ፣ ማኅበራዊ ግንኙነት ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥል የሚያግዝ በመሆኑ፤
በእርቅ የሚያልቁ ጉዳዮችን በተመለከተ ወጥ አሠራር እንዲኖር፤ በእርቅ አፈፃፀም ሂደት ባለሙያዎቸ ሊከተሉት የሚገባቸዉን ስነ-ስርዓት ማስቀመጥ እና ግልፅነት ያለዉ አሠራር መዘርጋት በማስፈለጉ፤
በቀድሞዉ ፍትሕ ሚኒስቴር ሲሰራበት የነበረዉ “በወንጀል ጉዳዮች የእርቅ አሠራር መመሪያ ቁጥር 14/2007 ከፌደራል ጠቅላይ ዐ/ሕግ አኳያ መቃኘት እና ማሻሻል በማስፈልጉ፤
የፌደራል ጠቅላይ ዐ/ሕግ በአዋጅ ቁጥር 943/2008 አንቀጽ 21(2) መሠረት ይህንን መመሪያ አዉጥቷል፡፡