የመመሪያ መለያ: 347/2013
ቀን: ታህሳስ 14፥ 2013 ዓ.ም.
Language: Amharic

ከጨርቅ የተሰራ የፊት መሸፈኛ ጭንብል አምራች የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እና የገበያ ፍቃድ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 347/2013

በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ መዛመትን በመግታት ሊያስከትል የሚችለውን አሉታዊ የጤና፤ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ተዕጽኖ መቀነስ በማስፈለጉ፤

የኮሮና ቫይረስን መዛመትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ጥቅም ላይ የሚውሉ የጤና ግብዓቶች ማሟላት የሚገባቸውን የጥራት ደረጃ ማሟላታቸውን በማረጋገጥ በተቀላጠፈ ሁኔታ ግብዓቶቹ የገበያ ፈቃድ አግኝተው ለተጠቀሚው እንዲደርሱ ለማድረግ፤

ለህክምና አገልግሎት በጤና ተቋማት ውስጥ ለጤና ባለሙያዎች ብቻ ጥቅም ላይ እንዲውል የሚመከር የህክምና የፊት መሸፈኛ ጭምብል ህብረተሰቡም ጭምር
እየተጠቀመ በመሆኑና በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የእነዚህ ምርቶች እጥረት መኖሩን ተከትሎ የምርቱ እጥረት እና የአጠቃቀም ችግር መፍታት
በማስፈለጉ፤

ይህንን ችግር ለመፍታት ጥቅም ላይ የሚውል በፋብሪካ ደረጃ ከጨርቅ የተሰራ የፊት መሸፈኛ ጭምብል ለህብረተሰብ ጥቅም ከመዋሉ በፊት ጥራቱ፤ ደህንነቱ እና ውጤታማነቱን ማረጋገጥ በማስፈለጉ፤

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በአዋጅ ቁጥር 1112/2011 አንቀጽ 71(2) እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012 ለማስፈጸም በወጣ የሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ አንቀጽ 4 (6 እና 7) መሠረት ይህን ጊዜያዊ የአሠራር መመርያ አውጥቷል፡፡

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF

ተጨማሪ መረጃዎች

መመሪያውን ያውርዱ

የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

Ethiopian Food and Drug Authority

Similar Directives

ሰኔ 18÷2018
ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር
Ministry of Trade and Regional Integration
ሰኔ 18÷2018
ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር
Ministry of Trade and Regional Integration