ቅርስ የሰው ልጅ የእድገት ሂደት፣ ባህልና ታሪክ መገለጫ ስለሆነ ህብረተሰቡን አሳታፊ ያደረገ የቅርስ ጥበቃና አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት ቅርሶች ላሉበት አካባቢ ህብረተሰብ ብሎም ለሀገር አቀፍ ዘላቂ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል በማስፈለጉ፤
በመሆኑም ባህል፣ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ ክልል ውስጥ የሚገኙ ቅርሶችን በመመዝገብ፣ በማጥናት፣ በመንከባከብ፣ በመጠበቅ፣ በማስጠበቅ እና በማልማት የቅርስነት እሴታቸው እንደተጠበቀ በማቆየት ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ቅርሶችን በብሔራዊ እና በክልል ቅርስነት መመደቢያ አዋጅ ቁጥር 839/2006 አንቀጽ 5 ንዑስ አንቀጽ (2) ፣ (3) እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 74/2014 ዓ.ም አንቀጽ 15 ንዑስ አንቀጽ (2) ተራ ፊደል (ሠ) መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡