ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል መሠረታዊ የሆኑ የምግብ አቅርቦቶችን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ ሆኖ እንዲገዛ ማድረግ የወጪ ጫናውን በማርገብ ረገድ ጠቀሜታ ያለው መሆኑ ስለታመነበት፤
ከዚህ በፊት በተለያዩ መመሪያዎች እቃዎች በጥቅል ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ መደረጋቸው ተጠቃሚ እንዲሆን የታሰበውን የህብረተሰብ ክፍል የማይጠቅም እርምጃ ሆኖ ከመገኘቱም በላይ የመንግሥትን ገቢ በመሸርሸር መንግሥት የድሃውን ህብረተሰብ ህይወት የሚለውጡ የማኅበራዊ እና ኤኮኖሚያዊ ልማት ስራዎችን ለመሥራት የሚያስችል ገቢ እንዳይኖረው ያደረገ በመሆኑ፤
በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 285/1994 (እንደተሻሻለ) አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ (2) 4 ለገንዘብ ሚኒስቴር በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የሚከተለው መመሪያ ወጥቷል።
WHEREAS, the blanket exemption from Value Added Tax previously granted to goods through various directives did not effectively benefit the intended sections of society, but instead reduced government revenue that could have been utilized for economic and social development activities to change the lives of the poor;
NOW THEREFORE, in accordance with the power vested in the Ministry of Finance under Article 8 sub article 2(4) of the Value Added Tax Proclamation No. 285/2002 (as amended), the following Directive is issued.