ለህብረተሰቡ በነጻ የሚሰጡ የትምህርት እና የጤና አገልግሎቶችን ለማስፋፋት እንዲሁም በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ችግር ሊይ የሚገኙ ወገኖችን ለመርዳት ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች የማኅበራዊ ልማት ቀረጥ የተጣለበትን ዓላማ ለማሳካት የሚያግዙ በመሆኑ ከቀረጥ ነጻ እንዲሆኑ ማድረግ ተገቢ መሆኑ ስለታመነበት፤
ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከቀረጥ እና ታክስ ነጻ የተደረጉ እቃዎች ከዚህ የቀረጥ ዓይነትም ነጻ እንዲሆኑ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የገንዘብ ሚኒስቴር ወደ ሀገር በሚገቡ ዕቃዎች ላይ የማኅበራዊ ልማት ቀረጥ ለማስከፈል የወጣ ደንብ ቁጥር 519/2014 አንቀጽ 6(3) መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡
WHEREAS, goods freely given to the public for improvement of education and health services and donated from abroad to assist citizens impoverished by natural and man-made calamities fulfill the intended purpose of the social welfare duty, it is deemed necessary to exempt them from the duty;
WHEREAS, it has become necessary to exempt goods that has been exempted from taxes and duties under international agreements to which Ethiopia is a party from such kind of duty too;
NOW, THEREFORE, Ministry of Finance issued this directive in accordance with Article 6(3) of Social Welfare Levy on Imported Goods Regulation No.519/2022.