ተቋማት አካል ጉዳተኞችን ተሳቢ ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ ስትራቴጂ ሊከተሉ እንደሚገባ ተገለጸ

It Was Stated Institutions Should Adopt a Service Delivery Strategy That Includes Persons with Disabilities

አለም አቀፉ የአካል ጉዳተኞች ቀን በፍትሕ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ደረጃ “አካታች የፈጠራ ሥራና ሽግግራዊ መፍትሄ ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ተደራሽነት” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡

ቀኑ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ31ኛ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ30ኛ ጊዜ ህዳር 24 ቀን 2015 ዓ/ም የተከበር ሲሆን የፍትሕ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ማለትም የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት፣ የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን፣ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የሲቭል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣንና የፌዴራል የፍትሕና የሕግ ኢንስቲትዩት ቀኑን በጋራ በመሆን በተለያዩ የንቅናቄ ተግባራት አክብረዋል፡፡

በፍትሕ ሚኒስቴር የሴቶችና ባለብዙ ዘርፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዳግማዊት አለምኔ በክብረ በዓሉ ተገኝተው ለታዳሚዎች መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም ቀኑ በፍትሕ ሚኒስቴር ደረጃ በየዓመቱ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ታጅቦ የሚከበር መሆኑን በመግለጽ ዘንድሮ በተለይም የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ በተሟላ ሁኔታ አካቶ ለመተግበር እንዲያስችል በማሰብ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ማክበር አሰፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ግንዘቤ በሚፈጥሩ ተግባራት ማክበር ተችሏል ብለዋል፡፡

ዳይሬክተሯ አያይዘዉም ፍትሕ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የሴቶችንና ሕፃናትን ጉዳይ አካተው እንደሚተገብሩት ሁሉ የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ አካታች በሆነ መልኩ ሊተገብሩና በተቋማቱ የሚገኙ አካል ጉዳተኛ ሠራተኞችንና የአካል ጉዳት ያለባቸው ተገልጋዮች በቂ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በአከባበሩም ከአካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን በመጡት አቶ ብርሃኑ ንጉሴ በአካል ጉዳተኞች እና አካል ጉዳተኛ ሰራተኞች መብት ዙሪያ ሰፊ የሆነ ገለጻ የተደረገ ሲሆን በገለጻውም እንደ ሀገር ወደ 21 ሚሊዮን የሚጠጉ አካል ጉዳተኞች እንዳሉና መንግስታዊም ሆኑ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት አካል ጉዳተኞችን ተሳቢ ያደረገ አገልግሎት አሰጣጥት ሊከተሉ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

አቶ ብርሃኑ ተቋማት አካል ጉዳተኞችን አስመልክቶ የወጡትን አዋጆች፣ ፖሊሶዎችና መመሪያዎች በተቀመጠው አግባብ ሊተገብሩና ከአተገባበሩ ጋር በተያያዘም በቂ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡

በተያዘው በጀት ዓመት የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ አካቶ ከመተግበር አንፃር በፍትሕ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የተከናወኑ ተግባራትን እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮችን በፍትሕ ሚኒስቴር የሴቶችና ባለብዙ ዘርፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በሆኑት ወ/ሪት ምዕራፍ ተስፋየሱስ በሪፖርት መልክ የቀረበ ሲሆን በተቋማቱ ለአካል ጉዳተኞች እየተሰጠ ያለው ትኩረት ከዚህ ቀደም ከነበረው ሁኔታ መሻሻል የታየበት ቢሆንም አሁንም ግን አንዳንድ ክፍተቶች የተሰተዋሉበት ስለመሆኑ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

ከተስተዋሉ ክፍተቶች መካከልም የስራ መግልገያ ህንፃዎችን የአካል ጉዳት ላለባቸው የተቋማቱ ሰራተኞች እንዲሁም ተገልጋዮች በሚፈለገው ደረጃ ምቹ አለማድረግ፣ አካል ጉዳተኛ ለሆኑ ሰራተኞች ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችንና ደጋፊ ቁሳቁሶችን ወይንም መገልገያ መሳሪያዎችን በበቂ ሆኔታ አለማሟላት እንዲሁም ቢሮዎችንና መሰብሰቢያ አዳራሾችን አመቺ አለማድርግ፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም በተቋማቱ መካከል ወጥ የሆነ አተገባበርና ወቅታዊ የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት በሚፈለገው ደረጃ አለመዘርጋት፣ የአካል ጉዳተኞችን ጉዳይ የሚከታተሉ የስራ ክፍሎችን በስው ኃይልም ሆነ በበቂ የሥራ ቁሳቁስ አለማሟልት እንዲሁም የተጠናከሩ እንዲሆኑ አለማድረግ ከተስተዋሉ ውስንነቶች መካከል ዋንኛዎች መሆናቸው የተለየ ሲሆን እንዚህን ክፍተቶች ለማስተካከል መሥራት እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

በአከባበሩ ወቅት በቀረበው ገለጻና ሪፖርት ዙሪያ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ተቋማቱ አካል ጉዳተኞችን ተሳቢ ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ ስትራቴጂ ሊከተሉ ይገባል ተብሏል፡፡

Tagged Under: accessibility accessibility standards amharic appeal civil liberties civil society organizations authority commission delivery disabilities disability disability inclusion disability rights employment federal federal tax appeal commission fundamental rights Human Rights Implementation Gaps inclusive Legal Frameworks persons persons with disabilities Rights Service Tax
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች