የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በፌዴራል ማረሚያ ፖሊስ መተዳደሪያ እና በፌዴራል እስረኞች አያያዝ ረቂቅ ደንቦች ዙርያ ከሚመለከታቸው የህግ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ

Federal Prison Administration Commission Holds Discussion on Draft Regulations for Federal Prison Police and Treatment of Federal Prisoners

በዛሬው ዕለት በአዳማ ከተማ የተደረገውን ይህን የውይይት መድረክ የአስጀመሩት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽር ጄኔራል ዳመነ ዳሮታ እንደተናገሩት ረቂቅ ደንቦቹ ለመንግሥት ቀርበው እንዲጸድቁ ከመጠየቃችን በፊት አስፈለጊ ግብቶችን እና የማስተካከያ እርምት ሂደቶችን እንዲያልፉ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የካቤኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ተስፋዬ ዳባን ጨምሮ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና የፍትሕ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሕግ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ረቂቅ ደንቦቹ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሕግ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ትቤሶ በዛብህ ቀርበዋል፡፡

ረቂቅ ደንቦቹ ከመጽደቃቸው በፊት በዘርፉ የካበት ዕውቀት እና ልምድ ባላቸው እና ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢው አስተያየት ተሰጥቶባቸው እና ዳብረው እንዲያልፉ መደረጉ የኮሚሽኑን ስራዎች በሕግ ማእቀፎች ታግዞ ወጥ የሆነ ውጤታማ ስራ መሥራት የሚያስችለው እንደሆነ ተነግሯል፡፡

ለውይይት የቀረቡ ሰነዶች የተሰጡ ግብቶችን በማካተት በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሚመለከተው የመንግሥት አካል ቀርበው ይጸድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፡- የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፌስቡክ ገጽ

Tagged Under: adama administration amhara region commission Consultation correctional services draft draft regulations federal Federal Prison Administration Commission Justice Justice Ministry legal Legal Consultation legal framework management ministry Penal Code Police policy reform prime prime minister's office prison prison regulations prisoner prisoner management regulations stakeholder Stakeholder Consultation
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች