ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት የመንገድ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ የበለጠ ለማጎልበት ዘርፉ አስተማማኝ፤ የተቀናጀ፤ ዘመናዊና ደኅንነቱ የተረጋገጠ ሆኖ እንዲራመድ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣
የመንገድ ትራንስፖርት አስተዳደር የመንግሥትን የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ፖሊሲ በአግባቡ ለመተግበር፤ የመንገድ ትራስፖርት እስከታችኛው የሀገራችን መዋቅር ድረስ ጠንካራ አፈጻጸምና የቁጥጥር ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግና የመንገድ ትራስፖርት ዘርፉን በቴክኖሎጂ ተደግፎ ተደራሽና አስተማማኝ እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችል ሥልጣንና ተግባር ማበጀት በማስፈለጉ፣
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•