በሀገሪቱ ውስጥ በዕቅድ ላይ የተመሰረተ የከተሞች ልማት እንዲኖር የከተማ ፕላን አገልግሎት እንዲስፋፋ ማድረግ በአጠቃላይ ብሔራዊ የልማት ጥረት ውስጥ ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ቁልፍ ተግባር ሆኖ በመገኘቱ፤
አዳጊ ከተሞች ወቅታዊ የሆኑ የፕላን መርሆዎችን በመከተል ጤናማና ዘላቂ የከተማ ልማት እንዲኖራቸው ማድረግ በከተማ ፕላን የሚመሩበትን ሥርዓት መደንገግና የአቅም ግንባታ ድጋፍ የሚሰጥበትን ሁኔታ ማመቻቸት ጠቃሚ ሆኖ በመገኘቱ፤
በሀገሪቱ ውስጥ ካለው ያልተማከለ አሠራር በሚጣጣም መልኩ የከተማ ፕላንን በሚመለከት የፌዴራል መንግሥቱን አካል እንደገና ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•